የኢትዮጵያ ሴቶች ድምጽ መጽሔት በየወሩ እየታተመ ለንባብ መብቃት ጀመረ፡፡

የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ሚኒስትር የኢትዮጵያ ሴቶች ድምጽ መጽሔት ለንባብ ማቅረቡን አስታወቀ፡፡

መጽሔቱ በዋነኝነት የሴቶች ልሳን ሆኖ የምታገለግል ሲሆን ሴቶች በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስኮች የሚገጥማቸውን ችግሮች፣ በየዘርፉ ተሳትፎና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡

እንዲሁም በተለያየ መስክ ውጤታማ የሆኑ ሴቶችን በአርአያነት የሚያቀርቡበት እንደሆነም ተገልጻል፡፡

መጽሔቱ በእንግሊዘኛ ቋንቋ እየተዘጋጀ የሚቀርብ ሲሆን ይህ የሆነበት ዋና ዓላማም ተቋሙ በዘርፉ የሚያከናውናቸውን ተግባራት ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ በማስተዋወቅ በቅርበት እየሰሩ የሚገኙ የልማት አጋራት የሚያደርጉትን እገዛና ድጋፍ ወደፊትም በበለጠ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማስቻል ነው ተብሏል፡፡

መጽሄቱ በመጀመርያ እትሙ ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከሰላም እሴት ግንባታ፣ እንዲሁም አለምን እያስጨነቀ ከሚገኘው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ አጀንዳዎች ይዞ ብቅ ብሏል፡፡

በሔኖክ ወ/ገብርኤል
ጥቅምት 4 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *