በኢትዮጵያ የተጀመረው ሕግ የማስከበር ስራ የአገሪቷን አንድነት በጠበቀ መንገድ እንዲካሄድ ሩሲያ አሳሰበች።

የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር መግለጫን ዋቢ አድርጎ ስፑትኑክ በድረገጹ ይዞት በወጣው ዘገባ የሩሲያ የረጅም ጊዜ ወዳጅ የሆነችው ጦርነቱ ኢትዮጵያ ግዛቷን እና አንድነቷን በማያናጋ መንገድ እንዲቋጭ ፍላጎት እንዳላት ገልጻለች።

ሚኒስቴሩ አክሎ እንዳለው ኢትዮጵያ የበርካታ ብሄሮች እና ሀይማኖቶች አገር እንደመሆኗ የፌደራል መንግስት እና የትግራይ ክልል የአገሪቱን አንድነት እና ዘላቂ ሰላም በጠበቀ መንገድ እንዲመክሩ በመግለጫው ጠቁሟል።

በኢትዮጵያ ከሳምንት በፊት የሰሜን ዕዝ ላይ በህዋሃት የደረሰበትን ጥቃት ተከትሎ የኢትየጵያ መንግስትም አጸፋውን በሃይል እርምጃ እየወሰደ ይገኛል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ክልል ጊዚያዊ የሽግግር መንግስት ማቋቋሙም ይታወሳል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አብይ አህመድ ባሳለፍነው አርብ የትግራይ ልዩ ሃይል ህገመንግስቱን በማስከበር ላይ ላለው የአገር መከላከያ ሰራዊት እጅ እንዲሰጡ የሰጡት የሶስት ቀናት ጥሪ ዛሬ ያበቃል።

የአገር መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ክልል ልዩ ሃይል እና ሚሊሻ በትናንትናው ዕለት የአላማጣ ከተማን እና ካባቢውን ሙሉ ለሙሉ ከትገራይ ልዩ ሃይል መቆጣጠራቸው ይታወሳል።

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ትኩስ ዜናዎችን፣ ስርጭቶችን፣ዜናዎችን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/ethiofm107dot8

በጅብሪል ሙሃመድ
ሕዳር 7 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *