አያት አደባባይ አካባቢ በሱቆች ላይ የተነሳው እሳት ወደ ሌሎች ሳይስፋፋ በቁጥጥር ስር ዋለ።

ትላንት ምሽት 3:00 ሰዓት ላይ አያት አደባባይ አካባቢ በሱቆች ላይ የተነሳው እሳት ወደ ሌሎች ሳይስፋፋ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ ።

በሱቆች ላይ የተነሳው የእሳት አደጋ በተደረገው ፈጣን ከፍተኛ ርብርብ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር ተችሏል ብሏል ከተማ አስተዳደሩ ።

የእሳት አደጋው ወደ ሌሎች ሱቆች እንዳይዛመት የእሳት እና አደጋ መከላከል ሰራተኞች ፣የአካባቢው ማህበረሰብ እና የጸጥታ አካላት ላደረጉት ርብርብ የከተማ አስተዳደሩ ምስጋና ይገባችኋል ብሏል።

ጥር 26 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *