የእስራኤል የጸረ ተባይ ተቋም በኢትዮጵያ ስራ ሊጀምር ነው፡፡

በጸረ ተባይ እርጭት ላይ የተሰማራው የእስራኤል የጸረ ተባይ ማዕከል ቅርንጫፍ ማዕከሉን በኢትዮጵያ ሊከፍት መሆኑን አስታዉቋል፡፡

ተቋሙ በዛሬው እለት ባወጣው መረጃ መሰረት በሚቀጥለው ወር በኢትዮጵያ የአየር ላይ ቫይረሶች እና ባክቴርያዎችን ለማጥፋት ስራ እጀምራለሁ ብሏል፡፡

ፕሮጀክቱ የንጹህ አየር ቴክኖሎጂ የተሰኘ መጠሪያ የተሰጠዉ ሲሆን፣መቀመጫው ኢትዮጵያ አድርጎ በ11 የአፍሪካ ሀገራት እንደሚተገበር ተቋሙ አስታውቋል፡፡

ይህ ቴክኖሎጂ የኮቪድ 19ኝን ስርጭት በተወሰነ መንገድ የሚከላከል እንደሆነም ነው የተገለጸው፡፡

በዚሁ ጉዳይ ዙሪያ ከሀገራቱ አምባሳዳሮች ጋር ስምምነት እንዳደረገ ያስታወቀው ተቋሙ፣ በሚቀጥለው ወር ቀጥታ ወደ ስራ እንደሚገባ ነዉ የገለጸዉ፡፡

የእስራኤል የጸረ ተባይ ተቋም በኢትዮጵያ በዋናነት በአየር ላይ የጸረ ተባይ እርጭት የሚያደርግ ቢሆንም፣ በጤናው ዘርፍ የሚታዩትን ችግሮች ለመፍታትም እንደሚሰራም ጨምሮ ገልጿል፡፡

ጀሩሳሌም ፖስት

በሔኖክ ወ/ገብርኤል
መጋቢት 23 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *