የሶማሊያ ፓርላማ የፕሬዝዳንት ፎርማጆ ስልጣን በሁለት አመት እንዲራዘም በአብላጫ ድምፅ አጸደቀ፡፡

ይህ አወዛጋቢ ልዩ ምርጫ በ 149 ድንፅ በሃገሪቱ የታችኛው ምር ቤት
የፀደቀ ሲሆን፣ ህግ ከመሆኑ በፊት ግን በላይኛው ምክር ቤት መፅደቅ አለበት ተብሏል፡፡

ፎርማጆ በታችኛው ምክር ቤት ረቂቅ መቀበላቸውን የገለፁ ሲሆን ከ 2 አመት በኋላ የሶማሊያ ህዝብ የራሱን ፕሬዝዳንት ይመርጣል ብለዋል፡፡

ተቃዋሚዎችና ጥቂት የክልል አመራሮች ይህን ረቂቅ ተቃውመውታል፡፡

የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትርና የአሁኑ የተቃዋሚ ጥምረት አባል ሀሰን አሊ ክሀይሬ ፤ ሀገሪቷ ቀውስ ውስጥ ነች ያሉ ሲሆን ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጣልቃ እንዲገባ አሳስበዋል፡፡

የፎርማጆ ስልጣን የካቲት 8 ማብቃቱን የሚያስታውሱት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ፤ ስልጣን ማራዘም ህገ ወጥ ነው፣ እኛ አንቀበለውም ሲሉ ተቃውሟቸውን ገልፀዋል፡፡

ቢቢሲ

በሔኖክ አስራት
ሚያዝያ 05 ቀን 2013 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *