በከተማዋ በጅምር ያሉ ያላለቁ እና ግንባታቸው አልቆም ሰው ያልገባባቸው ህንጻዎች የወንጀል መናኸሪያ እየሆኑ ነው የሚል ቅሬታ እየተነሳ ይገኛል።
በእነዚህ ህንጻዎች ተሰባስበው ያለ ስራ የሚቀመጡ ወጣቶች እንዳሉ ነዋሪው ጥቆማ እየሰጠን ነው ፤ ጥበቃም ይደረግልን ብለው ጥያቄ እያቀረቡ ነው ሲሉ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊው ኮማንደር ፋሲካ ፋንታ ለኢትዮ ኤፍ ኤም አረጋግጠዋል።
በጥቆማው መሰረትም ፖሊስ በተለይ ሰው ያልገባባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች እና ጅምር ህንጻዎች ላይ የተለየ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል ሲሉ ነግረውናል።
ህብረተሰቡም አካባቢውን በንቃት ከመጠበቅ ጎን ለጎን አጠራጣሪ እንቅስቃሴዎችን ሲያይ በአቅራቢያው ላለ የጸጥታ ሀይል እንዲያሳውቅም መልዕክት ተላልፏል።
መቅደላዊት ደረጄ
ነሐሴ 25 ቀን 2013 ዓ.ም











