የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤትም ወይዘሮ አዳነች አቤቤን የከተማው ከንቲባ በማድረግ መርጧል፡፡

ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ከነሀሴ 12 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ በመሆን ያገለገሉ ሲሆን አሁንም በድጋሚ ከተማዋን በከንቲባነት እንዲመሩ ተመርጠዋል፡፡

ወ/ሮ አዳነች ከተማዋን ከ 12 ወራት በላይ በምክትል ከንቲባ ማእረግ እየመሩ የሚገኙ ሲሆን ፣ ምክር ቤት በዛሬው እለት ባካሄደው ጉባዔም ከንቲባ አድርጎ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በከንቲባነት ሾሟል፡፡

ወይዘሮ አዳነች አቤቤ የአዳማ ከተማ ከንቲባ፤ የገቢዎች ሚኒስትር፤ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በመሆን አገልግለዋል፡፡

በጅብሪል ሙሃመድ
መስከረም 18 ቀን 2014 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *