በኤሌክትሪክ እና በአነስተኛ የነዳጅ ፍጆታ የሚሰሩ 25 ሺህ ተሽከርካሪዎችን ላቀርብ ነው አለ

አቤት ትራንስፖርት በሚቀጥሉት 5 አመታት 25 ሺህ በኤሌክትሪክ እና አነስተኛ የነዳጅ ፍጆታ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ለማቅረብ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡

ተሽከርካሪዎቹ የ2021 የጀርመንና የሩሲያ ስሪት መሆናቸውን የድርጅቱ ምክትል ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ሙሉ ደሜ ተናግረዋል፡፡

ተሽከርካሪዎቹ ባለ 5 ፤7 እና 26 መቀመጫ ያላቸውና ለህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚውሉ ናቸው ተብሏል፡፡

መግዛት የሚፈልጉ ሰዎች ከ 30 ሺህ ብር ጀምሮ የወረፋ መጠበቂያ ክፍያ በመክፈል ይስተናገዳሉ፡፡

ድርጅቱ በ7.7 ቢሊዮን ብር ካፒታል ስራውን እንደጀመረ የተገልጸ ሲሆን፣ ተሽከርካሪዎቹ የሚገጣጠሙት ደግሞ በኮምቦልቻ ከተማ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

60 ሺህ ዜጎች በቀጣዮቹ 5 አመታት በአቤት ትራንስፖርት በኩል የስራ እድል ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተነግሯል፡፡

ሔኖክ ወ/ገብርኤል
ጥቅምት 17 ቀን 2014 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *