አቤት ትራንስፖርት በሚቀጥሉት 5 አመታት 25 ሺህ በኤሌክትሪክ እና አነስተኛ የነዳጅ ፍጆታ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ለማቅረብ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡
ተሽከርካሪዎቹ የ2021 የጀርመንና የሩሲያ ስሪት መሆናቸውን የድርጅቱ ምክትል ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ሙሉ ደሜ ተናግረዋል፡፡
ተሽከርካሪዎቹ ባለ 5 ፤7 እና 26 መቀመጫ ያላቸውና ለህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚውሉ ናቸው ተብሏል፡፡
መግዛት የሚፈልጉ ሰዎች ከ 30 ሺህ ብር ጀምሮ የወረፋ መጠበቂያ ክፍያ በመክፈል ይስተናገዳሉ፡፡
ድርጅቱ በ7.7 ቢሊዮን ብር ካፒታል ስራውን እንደጀመረ የተገልጸ ሲሆን፣ ተሽከርካሪዎቹ የሚገጣጠሙት ደግሞ በኮምቦልቻ ከተማ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
60 ሺህ ዜጎች በቀጣዮቹ 5 አመታት በአቤት ትራንስፖርት በኩል የስራ እድል ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተነግሯል፡፡
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
ጥቅምት 17 ቀን 2014 ዓ.ም











