በበጀት አመቱ ባለፉት አምስት ወራት ከ7 መቶ 33 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማሰባሰቡን የአዲስ አበባ የአሽከርካሪና ተሸከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

በ2014 በጀት አመት 875 ሚሊዮን ብር ገቢ ለማሰባሰብ አቅዶ ባለፉት አምስት ወራት ብቻ 733 ሚሊዮን 875ሺ 5 መቶ19 ብር ገቢ በማሰባሰብ የእቅዱን 83 በመቶ ማሳካት መቻሉን የአዲስ አበባ የአሽከርካሪና ተሸከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን አስታውቋል፡፡
የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ገቢውን ከመንጃ ፍቃድ ፤ ከሰሌዳ ፤ ከቦሎ ፤ ከተሸከርካሪ ስም ዝውውርና ከተያያዥ አገልግሎቶች በማሰባሰብ በግማሽ በጀት አመት ውስጥ እቅዱን በላቀ ሁኔታ ማሳካቱን ገልጿል፡፡

በቀጣይም ተቋሙ የሚሰጣቸውን የአገልግሎት ዘርፎች በማስፋትና የገቢ አሰባሰብ ዘርፎቹን በማዘመን እቅዱን በእጥፍ ለማሳካት እንሚሰራም አስታውቋል።
ህዳር 28 ቀን 2014 ዓ.ም
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያውያን

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *