ፕ/ር ካሣሁን ብርሀኑ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም ዐቀፍ ግንኙነት (PSIR) ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ የነበሩት ፕ/ር ካሣሁን ብርሀኑ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ፕ/ር ካሣሁን በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ የካቲት 15/2014 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት አሳውቋል።

ፕ/ር ካሣሁን ላለፉት 36 ዓመታት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነትና ተመራማሪነት እንዲሁም በልዩ ልዩ ከፍተኛ የኃላፊነት ዕርከኖች አገልግለዋል።

በአገር ውስጥ እና ከአገር ውጪ የተለያዩ ማኅበራዊ አገልግሎቶችን በማበርከትም ይታወቁ ነበር፡፡

የቀብር ስነ ስርዓታቸው ነገ የካቲት 16 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 በየካ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት ይፈፀማል፡፡

የካቲት 15 ቀን 2014 ዓ.ም

ኢትዮ ኤፍ ኤም የኢትዮጵያውያን

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *