የሁውቲ ታጣቂዎች በየመን ለማካሄድ በታቀደው ድርድር ሳኡዲ አደራዳሪ መሆን አትችልም ብለዋል

ለአመታት በየመን እየተካሄደ ካለው ጦርነት ጋር በተያያዘ ስሟ በሰፊው የሚነሳው ሳኡዲአረቢያ የየመንን ሃይሎች ለማደራደር በሚደረገው ጥረት ምንም አይነት ድርሻ ሊኖራት እንደማይገባ አስታውቋል

ሁውቲ ይህን ያለው የድርድር ሂደቱ በሳኡዲ መዲና ሪያድ ለማድረግ መታቀዱን በመቃወም ነው

የሁውቲ አብዮታዊ ከፍተኛ ኮሚቴ ሊቀመንበር እንዳስታወቀው ከሆነ ሳኡዲ ከተዋጊዎች አንዷ ናትና ለማሸማገል አትችልም ብለዋል

በሳኡዲ የሚመራው ጦር ለአመታት በጦር ውርጅብኝ ያረሳትን የመንን መልሶ ለማቋቋም ድርድር ለማካሄድ ሳኡዲ አረቢያ የሁውቲ ታጣቂዎችን ለመጋበዝ አቅዶ ነበር

ድርድሩ እንዲካሄድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም ድጋፉን ሲሰጥ መቆየቱን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

አብዱልሰላም አንሳር
መጋቢት 07 ቀን 2014 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *