በአንድ ወቅት ከፍተኛ የቦታ ጥበት አጋጥሞት የነበረው የካ ኮተቤ ሆስፒታል ዛሬ አንድም የኮቪድ 19 ታካሚ እንደሌለው አስታወቀ።

ሆስፒታሉ ትላንትና የመጨረሻውን የኮቪድ-19 ታካሚ በሰላም ወደ ቤቱ መሸኘቱን እና ሆስፒታሉ በሁለት አመት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ያለ ኮቪድ19 ታካሚ ውሎ ማደሩን የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጁ ዶ/ር ያሬድ አግደው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።

” በትናንትናው ዕለት የመጨረሻውን ታካሚ ወደ ቤቱ በሰላም ሸኝተናል ” ያሉት ዶ/ር ያሬድ ” በሁለት አመት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ሆስፒታሉ ያለ ኮቪድ 19 ታካሚ ውሎ ማደሩን ገልፀዋል።

” ከዚህ በኋላ ሀገርን በሚጎዳ መልኩ የኮቪድ 19 ማዕበል በሀገራችን በድጋሚ እንዳይከሰት ሁላችንም የድርሻችን መወጣት ይኖርብናል ” ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያን

ሚያዝያ 28 ቀን 2014 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *