የእስራኤል ፖሊሶች ከፍልስጤማውያን ጋር ግጭት መፍጠራቸው ተሰማ።

በተከበረው የእስራኤል የነጻነት ቀን፣ ፖሊስ የፍልስጤም ተቃዋሚዎች ላይ እርምጃ በመውሰዱ በእየሩሳሌም አል-አቅሳ መስጊድ ሁከት መቀስቀሱን አር ቲ ኒውስ
ዘግቧል ።

በክብረ በዓሉ እለት እስራኤል ፍልስጤማዊያን በሚገኙበት ቀጠና የእስራኤል ሰንደቅ አላማ እንዲውለበለብ የሚያዙ መመሪያዎቹን አውጥታ እንደነበር ተገልጿል ።

ነገር ግን ፍልስጤማውያን ለወጣው መመሪያ ተገዢ ከመሆን ይልቅ ግድየለሽነትን እያሳዩ ነው በሚል በእስራኤል ሃይሎች እርምጃ ተወስዷል ተብሏል ።

እስራኤልም አመፁን ያስጀመሩት ፍልስጤማዊያን መሆናቸውን በመግለፅ ፤በእሳት እየተጫወቱ እና ቀጣናውን ወደ ከፋ ደረጃ እንዲሄድ እያደረጉ ነው ስትል አስጠንቅቃለች ።

የአይን ምስክሮች ደግሞ አመፁን ያስጀመሩት ፍልስጤማውያን ናቸው የሚለውን ሃሳብ ከእውነት የራቀ ነው ብለዋል ።

በተወሰደው እርምጃ የሞቱ አልያም ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ይኑሩ አይኑሩ መረጃው መረጃው ያለው ነገር የለም።

በመሳይ ገ/ መድህን

ሚያዝያ 28 ቀን 2014

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *