ሱዳን ከመፈንቅለ መንግስት ወዲህ ተጥሎ የነበረውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አነሳች።

የሱዳን ወታደራዊ መንግስት ከስድስት ወራት በፊት በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ከተቆጣጠረ በኋላ የጣለውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አንስቷል እንደ ቢቢሲ አፍሪቃ ዘገባ።

የሀገሪቱ ገዥ የፀጥታና መከላከያ ምክር ቤት በወታደራዊ መሪው ጄኔራል አብደል ፈታህ አል ቡርሃን በተመራው ስብሰባ ላይ ነው ይህ ውሳኔ የተላለፈው ብሏል፡፡
ርምጃው ትክክለኛውን የውይይት ሁኔታ ለመፍጠር ያለመ ነው ብሏል።

በጥቅምት ወር ከተካሄደው መፈንቅለ መንግስት በኋላ በወታደራዊው መንግስት ላይ የሚካሄደው ተቃውሞ አሁንም ቀጥሏል።
በቅርብ ቀናት የጸጥታ ሃይሎች የተቃውሞ እንቅስቃሴ መሪዎችን ኢላማ በማድረግ በርካታ ተቃዋሚዎችን በቁጥጥር ስር አውለዋል።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ግንቦት 22 ቀን 2014 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *