“ምን ልታዘዝ አዲስ”የተሰኘው መተግበሪያ የባለሙያ አቅርቦት እና ማንኛውንም አገልግሎቶችን በፍጥነት እንዲያገኝ የሚረዳ ነው ተብሏል ።
ዋና ስራ አሰፈፃሚው አቶ ሱራፌል ተምትሜ እንዳሉት ለረጅም ጊዜ ለማህበረሰቡ ምን ያህል ጠቀሜታ ይሰጣል በሚል ሰፊ ጥናት ተደርጎበታል ።
ከተደራሽነት አንፃር ሁሉንም የሙያ ዘርፍ እና ተቋማትን ተደራሽ ያደርጋል የቸባለ ሲሆን፣ባለሞያዎች ሳይንገላቱ እና አገልግሎቶች ሳይስተጓጎሉ ስራዎች እንዲሳለጡ ያደርጋል ተብሏል ።
አገልግሎቱን መጠቀም የሚፈልጉ ተቋማትም ሆኑ ባለሞያዎች መተግበሪያውን በማውረድ መመዝብ ካልሆነም በ “625” ላይ መደወል እንደሚችሉ ተገልጿል።
ከዚያም በኃላ ደንበኞች በፈለጉበት ሆነው በሙያቸው ወደ ስራ መሰማራት እና አገልግሎት ፈላጊዎች የፈለጉትን ማግኘት ይችላሉ ።
ከአገልግሎቶች መካከል ፣የዲሽ ስራ፣ቲቪ እና ፍሪጅ ጥገና ፣የብየዳ ስራ ፣የቀብር ማስፈፀም እና ሌሎችም በረካታ አገልግሎቶች ተካተዋል።
ከነዚህም በተጨማሪ አገልግሎቱ ለግንባታው ዘርፍ ትልቅ አቅም ይፈጥራል ተብሏል።
በመሳይ ገ/መድህን
ሰኔ 09 ቀን 2014 ዓ.ም











