በሳምንቱ ከ2ሺህ በላይ ዜጎች ከሳዉዲ አረቢያ ወደ አገራቸው ተመልሰዋል ተባለ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ከሳዉዲ አረቢያ 2158 ዜጎችን ማስመለስ ተችሏል።

ተሰናባቹ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ ከሳውዲ አረቢያ ዜጎችን የማስመለሱ ጥረት ይቀጥላል ብለዋል ።

በሳምንቱ ከሳውዲ ከተመለሱ ዜጎች በተጨማሪም ከታንዛኒያ 5መቶ ዜጎችን ማስመለስ እንደቸቻለ አምባሳደር ዲና አስታውቀዋል።

በቀጣይም በለያዩ ሀገራት በችግር ላይ የሚገኙ ዜጎችን ወደ አገራቸው ለማስመለስ ይሰራል ብለዋል ።

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ከቃል አቀባይነታቸው ተነስተው የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ዳይሬክተር ጄነራል ሆነው መሾማቸው ይታወሳል ።

በምትካቸው በኬንያ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር መለስ አለም ተሾመዋል።

በአባቱ መረቀ

ሰኔ 16 ቀን 2014 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *