የካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪስ መትሴፔ ለአንድ ቀን የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ መግባታቸውን ካፍ ኦንላይን ጽፏል፡፡
በቆይታቸው ከፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ፣ ከባህል እና ስፖርት ሚኒስትሩ ቀጄላ መርዳሳ ፣ ከእግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ ጂራ እና ስፖርቱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ይገናኛሉ፡፡
ሞትሴፔ ከእግር ኳስ ክለቦች ፕሬዝደንቶች ጋር በመወያየት ጉብኝታቸውን እንደሚያጠናቅቁም ተገልጿል፡፡
በአቤል ጀቤሳ
ሐምሌ 06 ቀን 2014 ዓ.ም











