የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስተር ለዩክሬን የ2.63 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገቡ፡፡

አዲሷ የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስተር ሊዝ ትረስ ለዩክሬን ጦርነት ድጋፍ የሚሆን የ2.63 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ እናደርጋለን ብለዋል፡፡

ይህ ገንዘብ አገሪቱ ከዚህ በፊት ኪየቭ ከሩሲያ ጋር ለምታርገዉ ጦርነት ከመደበችዉ የገንዘብ መጠን እንደሚበልጥ ተነግሯል፡፡

ሊዝ ትረስ እንግሊዝ በእያንዳንዱ እርምጃ ከዩክሬን ጎን ሆና ትቀጥላለች ሲሉ ቃል አቀባይ መናገራቸዉን ፋይናንሺያል ታይምስ ዘግቧል፡፡

ለንደን አ.ኤ.አ በ2022 ለኪየቭ ካደረገችዉ የ2.63 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ አኳያ ለዩክሬን ትልቅ ወታደራዊ ድጋፍ ያደረገች አገር መሆኗን መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡

በቤዛዊት አራጌ
መስከረም 10 ቀን 2015 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *