ለጎረቤት ሃገራት ከተሸጠ የኤሌክትሪክ ሃይል የተገኘ
ገቢ፡-

• ለጎረቤት ሀገራት ከተሸጠ የኤሌክትሪክ ሃይል ከ13 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል
• ገቢዉ የተገኘዉ በተያዘው በጀት ዓመት ሁለት ወራት ለሱዳንና ጂቡቲ ከቀረበ የኤሌክትሪክ ኃይል ነዉ፡፡

• ባለፉት ሁለት ወራት ለሱዳን እና ጂቡቲ ከ349 ነጥብ 56 ሚሊየን ኪሎ ዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ታቅዶ ነበር፡፡

ማቅረብ የተቻለዉ ግን 232 ነጥብ 76 ሚሊየን ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሲሆን ከዚህም 13 ነጥብ 04 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ሽያጭ በማከናወን የዕቅዱን 70 ነጥብ 29 በመቶ ማሳካት ተችሏል ተብሏል፡፡

• በሁለቱ ወራት ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ከተገኘው ገቢ በተጨማሪ ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ከ2 ነጥብ 74 ቢሊየን ብር በላይ ተገኝቷል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *