ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በሰሜን ኢትዮጵያ የይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸው ቦታዎች “በሀገሪቱ ህግ ብቻ ምላሽ” እንደሚያገኙ አስታወቁ

በደቡብ አፍሪካ ላይ በነበረው ድርድር ኢትዮጵያ የቀረበችው ሀሳብ “መቶ በመቶ ተቀባይነት አግኝቷል” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ።

የይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸው ቦታዎችም “በሰላም እና በድርድር እንዲሁም በሀገሪቱ ህግ ብቻ ምላሽ እንዲያገኙ” ከስምምነት ላይ ተደርሷል ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል በትላንትናው ዕለት በደቡብ አፍሪካ የተደረገውን የሰላም ስምምነት አስመልክቶ ዛሬ ሐሙስ ጥቅምት 24 በአርባ ምንጭ ስቴድየም ባደረጉት ንግግር ነው።

አብይ በዚሁ ንግግራቸው፤ የሰላም ስምምነቱን ለኢትዮጵያ “ታላቅ ዕድል ነው” ብለዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ከተዘረዘሩት የትላንቱ የሰላም ስምምነት አንኳር ነጥቦች መካከል፤ በተፋላሚ ወገኖች “የይገባኛል ጥያቄ” የሚነሳባቸው ቦታዎችን የተመለከተው ይገኝበታል።

“በአንዳንድ ቦታዎች ላይ የይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸው እና አከራካሪ የሆነ ቦታዎች፤ ዳግም የሰው ልጆችን ህይወት ሳይነጥቁ፤ በሰላም፣ በድርድር እና በሀገሪቱ ህገ መንግስት መሰረት ብቻ ምላሽ እንዲያገኙ በሁለቱም ወገኖች ከመተማመን ተደርሷል” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

በአባቱ መረቀ

ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *