የሀገር ምልክት የሆኑትን አርበኞች ማክበርና መደገፍ ይገባል ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ገለጹ፡፡
የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ዓመታዊ ግምገማውን በባሕር ዳር ከተማ እያካሄደ ነው።
ርዕሰ መሥተዳድር ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ጀግኖች አርበኞች የውጪ ወራሪዎችን በራሳቸው ትጥቅና ስንቅ ታግለው ማሸነፋቸውን አስታውሰው ዛሬም ቢሆን አርበኞች የአሁኑን ትውልድ እያስተማሩ ይገኛሉ ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡
አርበኞችን ማክበርና መደገፍ እንደሚገባ ጠቁመው መንግሥት ብቻ ሳይሆን ግለሰቦች እና ባለሀብቶች ተገቢውን ድጋፍ ሊያበረክቱላቸው እንደሚገባም አሳስበዋል።
የክልሉ መንግሥት ለጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር የሚሆን አደባባይ በባሕር ዳር ከተማ እንደሚሰይምም ቃል ገብተዋል።
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ታህሳስ 11 ቀን 2015 ዓ.ም