የሃይማኖት አባቶች ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በመልዕክታቸውም÷ የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል የፍቅር እና የትህትና መሠረት በመሆኑ ክርስቲያን ምዕመኑ ርስበርስ በመፋቀር እና በመዋደድ በተግባር ሊተረጉመው ይገባል ሲሉ የሃይማኖት አባቶች አሳስበዋል፡፡

እግዚአብሔር ሰው ሆኖ ወደዚች ምድር መምጣቱ ለሰው ልጅ ያለውን ፍቅር ማሳያ በመሆኑ እኛም እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ያሳየውን ፍቅር ማሳየት ይገባናል ብለዋል።

ርስበርስ መዋደድ በሰላምና በፍቅር መኖር አምላካዊ ትእዛዝ ነውና በመንፈሳዊና አለማዊ የስራ ሃላፊነት የምንገኝ ሰዎች የእግዚአብሔር ትእዛዙን ማክበር ግዴታችን ነው ብለዋል።

በዓሉ የትህትና እና የፍቅር በዓል እንደመሆኑ ክርስቲያን ምዕመኑ በተለያየ ምክንያት የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብ እና ካለው በማካፈል በዓሉን አብሮ ማሳለፍ ይገባል ሲሉም አሳስበዋል።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ታህሳስ 28 ቀን 2015 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *