የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለስራ ፈጣሪዎች ያለማስያዣ ድጋፍ ሊያደርግ ነዉ ተባለ።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሀሳብ ያላቸዉ ሀሳባቸዉ ተወዳዳሪ ሆኖ ላሸነፍ እና ወደምርት ቢገቡ አዋጪ ይሆናሉ ብሎ ላሰባቸዉ ስራ ፈጣሪዎች፣ ያለማስያዣ ድጋፍ ለማድረግ ከስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር መስማማቱ ተገልጿል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ስምሪት እና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደገለጹት፣የስራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታት በርካታ ስራ እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
ከልማት ባንክ ጋር የተደረገዉ ስምምነትም ለስራ ፈጣሪዎቾ አበረታች ነዉ ብለዋል።

ተቋማቸዉ ሌሎች መንገዶችንም እየተመከተ እንደሚገኝ የተናገሩት አቶ ንጉሱ፣ አሰራሮችን፣ፖሊሲዎችን እና ስትራቲጂዎችን በመቀየስ ላይ ይገኛል ብለውናል።
ሀገሪቱ የነበራትን የጥቃቅንና አነስተኛ እንዲሁም መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ስትራቴጂ ለሶስተኛ ጊዜ የመከለስ ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል ሚኒስቴር ድኤታዉ።
ይሁን እንጂ ስትራቴጂዉ ወደ ፖሊሲነት ማደግ ስላለበት በፖሊሲ ደረጃ ተቀርፆ፣ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲፀድቅ ይላካል መባሉን ኢትዮ ኤፍ ኤም ሰምቷል።

በአቤል ደጀኔ

ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *