ምክር ቤቱ  የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሹመትን አፀደቀ

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ስብሰባው ወ/ሮ ምዕላተወርቅ ሀይሉን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ አድርጎ ሾሟል ።

ወ/ሮ ምዕላተወርቅ ሀይሉ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የፅ/ቤት ሀላፊ ሆነው እያገለገሉ እንደሚገኙ በምክር ቤቱ የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚንስትር አቶ ተስፋዬ በልጅጌ ካቀረቡት ግለ ታሪካቸውን መረዳት ተችሏል።

ምክር ቤቱ ወ/ሮ  ምዕላተ ወርቅ ሀይሉን የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ አድርጎ በአንድ ድምፀ ተዓቅቦ በአበላጫ ድምፅ በውሳኔ ቁጥር 2/2016 ሆኖ አፅድቋል።

የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው የተሾሙት ወ/ሮ  ምዕላተ ወርቅ ሀይሉ የተሰጣቸውን ሃላፊነት በታማኝነት፣ በትጋትና  በብቃት ለመወጣት በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ-ማሃላ ፈጽመዋል።

ታህሳስ  9  ቀን 2016 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *