የአዉሮፓ ህብረት ከሩሲያ የሚያስገባዉን የጋዝ መጠን ከ40 ወደ 26 በመቶ መቀነሱን ተናግሯል፡፡

በአንድ አመት ግዜ ዉስጥ የአዉሮፓ ህብረት ከሩሲያ የሚያስገባዉን የጋዝ መጠን ከ40 ወደ 26 በመቶ መቀነሱን ተናግሯል፡፡

የአዉሮፓ ህብረት ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ሌየን እንደገለጹት ከአምናዉ ጋር ሲነጻጸር በዚህ ዓመት ከሩሲያ የሚገባዉን የጋዝ መጠን መቀነሳቸዉን ተናግረዋል፡፡

ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለጹት አምና 40 በመቶ የሚሆነዉ የአዉሮፓ ህብረት ሀገራት የነዳጅ ፍላጎት በሩሲያ የተሟላ ሲሆን፣ዘንድሮ ግን ወደ 26 በመቶ ዝቅ ለማድረግ ችለናል ብለዋል፡፡

የአዉሮፓ ህብረትን ፖሊሲ በተለይ ደግሞ በሀይል አቅርቦቶች ላይ ያለዉን ጉዳይ ‹‹በትክክለኛዉ መንገድ እየሄደ ነዉ›› ሲሉ የገለጹ ሲሆን ፤ በተጨማሪም ‹‹አዉሮፓ ህብረትን በድጋሚ በሀይል መሙላት›› ለተሰኘዉ አዲሱ ዕቅድ ፈጣን ለዉጦች እንዲያስመዘግብ በጋራ መስራት እንዳለባቸዉም አጽንኦት ሰጥተዉ ተናግረዋል፡፡

ይህ አዲሱ ዕቅድ በሩሲያ ነዳጅ ላይ ጥገኛ የሆነዉን የአዉሮፓ ህብረትንከጥገኝነቱ ለማላቀቅ፤ በዉስጡ የሚገኙ የተለያዩ ፋብሪካዎች እና ኩባንያዎች የጸሀይ ሀይል ላይ ትኩረታቸዉን አድርገዉ እንዲሰሩ የሚያስገድድ መሆኑ አር ቲ ኒዉስ
ዘግቧል፡፡

በእስከዳር ግርማ
ግንቦት 10 ቀን 2014 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *