የመስቀል በአልን ምክንያት በማድረግ ከታሪፍ በላይ በጠየቁ 50 አሽከርካሪዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ገለጸ፡፡

የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ከመስቀል በአል አከባበር ጋር በተያያዘ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ እየወሰድኩ እገኛለሁ ሲል አስታውቋል፡፡

በፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን የመለስተኛ እና አነስተኛ መናሃሪያ የአዲስ ክፍለ ከተማ መናሃሪያ የቡድን መሪ አቶ ውብሸት ደመላሽ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት የመስቀልን በዓል ለማክበር ከመዲናዋ ውደ ተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በሚንቀሳቀሱ ተጓዞች ላይ የሚደረግን የታሪፍ ጭማሪ ለመቆጣጠር አዲስ አሰራር ዘርገተን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል፡፡

ከቁጥጥር ስራው ጋር በተያያዘ ባለፉት ሁለት ቀናት ብቻ ከታሪፍ በላይ በጠየቁ 50 ያህል አሽከርካሪዎች ላይ የቅጣት እርምጃ እንደተወሰደባቸው አቶ ውብሸት ነግረውናል፡፡

እንደ ዚሁም በሁለት ቀናት ውስጥ 110 ብር የነበረው የወልቄጤ መደበኛ የታሪፍ ዋጋ ላይ 300 በጠየቁ 5 ያህል አሽከርካሪዎች እስከ 2ሺህ ብር የሚደረስ ቅጣት ተላልፎባቸዋል ብለውናል፡፡

በበአሉ የተሸከርካሪ እጥረት እንዳይከሰት ባለስልጣን መስራቤቱ እንደ ርቀታቸው እና እንደ አካባቢው ሁኔታ በተቀመጠው መመሪያ መሰረት ከ35 ከመቶ እስከ 50 በመቶ የታሪፍ ጭማሪ ተደርጎ የህብረተሰቡን እንግልት ለማስቀረት እየሰሩ እንደሆነም አቶ ውብሸት ተናግረዋል፡፡

አሁን ላይ በየቀኑ እስከ 1ሺህ ተሽከርካሪዎች ለስምሪት እንደሚወጡም ነው ሀላፊው ለጣቢያችን የተናገሩት፡፡

ከህጻናት ጋር ተያይዞ የሚፈጠረው አለምግባባት በተመለከተም እድሜያቸው 7 አመት የሆኑ ህጻናት በእናቶቻቸው ወይም በሞግዚቶቻቸው አማካኝነት ሳይከፍሉ ሊጓዙ እንደሚችሉ ተናግረው እድሜያቸው 12 የሆናቸው ደግሞ በግማሽ ከፍለው መጓዝ ይችላሉ ሲሉ አቶ ውብሸት ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን ቻናላችንን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን https://t.me/ethiofm107dot8 ይቀላቀሉ።
በሔኖክ ወ/ገብርኤል
መስከረም 13 ቀን 2014 ዓ.ም

FacebooktwitterredditpinterestlinkedinmailFacebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *